Online Admission የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

28th January, 2026

ቀን: ጥር 19/2018 ዓ/ም


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የመስክ ምልከታ ተካሄደ።


የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ  የስራ ሂደት  በኮሌጁ  የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚደረግላቸው  ኢንተርፕራይዞች የድጋፍ ሁኔታ ዘርፉን ከሚመሩ ባለሙያዎች  ጋር  በመሆን የመስክ ምልከታ አካሄዷል፡፡


የምልከታው ዋና ዓላማ  ኮሌጁ በአራቱንም የድጋፍ ማዕቀፍ ፍላጎትን መሠረት ያደረገ  የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አሰጣጥ ሂደቱን ለመገምገምና የቀጣይ የትኩረት  አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን የሆኑት ሙሉጌታ አለሙ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
በምልከታው ኢንተርፕራይዞች በኮሌጁ የሚሰጠው ፍላጎትን መሰረት ያደረገ  የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ  ምርት እና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንደሚረዳ ገልፀዋል።


‹‹የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሙኒኬሽን ››

.

Copyright © All rights reserved.

Created with